ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ዘኁልቍ 21:12-20 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

12. ከዚያም ተጒዘው በዘሬድ ሸለቆ ሰፈሩ።

13. ከዚያም ተነሥተው እስከ አሞራውያን ግዛት በሚዘልቀው ምድረ በዳ ባለው በአርኖን አጠገብ ሰፈሩ፤ አርኖን በሞዓብና በአሞራውያን መካከል የሚገኝ የሞዓብ ወሰን ነው።

14. እንግዲህ በእግዚአብሔር (ያህዌ) የጦርነት መጽሐፍ እንዲህ ተብሎ የተጻፈው በዚሁ የተነሣ ነው፤“ … በሱፋ ውስጥ የሚገኘው ዋሄብአርኖንና

15. ወደ ዔር የሚወስዱትበሞዓብ ድንበርም የሚገኙትየሸለቆች ተረተሮች።”

16. ከዚያም እግዚአብሔር (ያህዌ) ለሙሴ፣ “ሰዎቹን በአንድነት ሰብስባቸውና ውሃ እሰጣቸዋለሁ” ወዳለበት ብኤር ወደተባለው የውሃ ጒድጓድ ጒዞአቸውን ቀጠሉ።

17. ከዚያም እስራኤል ይህን መዝሙር ዘመረ፤“አንተ ምንጭ ሆይ ፍለቅ!እናንተም ዘምሩለት፤

18. ልዑላን ለቈፈሩት፣የሕዝብ አለቆች በበትረ መንግሥታቸውና በበትሮቻቸው ላጐደጐዱት፣የውሃ ጒድጓድ ዘምሩለት።”ከዚህ በኋላ ከምድረ በዳው ወደ መቴና ሄዱ፤

19. ከመቴና ወደ ነሃሊኤል፣ ከነሃሊኤልም ወደ ባሞት፣

20. ከባሞትም ፈስጋ ላይ ሆኖ ምድረ በዳው ቊልቊል ወደሚታይበት በሞዓብ ወደሚገኘው ሸለቆ ተጓዙ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ዘኁልቍ 21