ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ዘኁልቍ 4:16-20 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

16. “የካህኑ የአሮን ልጅ አልዓዛር በመብራቱ ዘይት፣ ደስ የሚያሰኝ ሽታ ባለው ዕጣን፣ ዘወትር በሚቀርበው በእህል ቍርባንና በቅብዐ ዘይቱ ላይ ኀላፊነት ይኖረዋል፤ እንደዚሁም ማደሪያውንና በውስጡ ያለውን ሁሉ መቅደሱንና ዕቃዎቹን ጭምር ይጠብቃል።”

17. እግዚአብሔር (ያህዌ) ሙሴንና አሮንን እንዲህ አላቸው፤

18. “የቀዓት ጐሣዎች ከሌዋውያን ተለይተው እንዳይጠፉ፤

19. ወደ ንዋየ ቅዱሳቱ በሚቀርቡበትም ጊዜ በሕይወት እንዲኖሩ እንጂ እንዳይሞቱ አንተ ይህን አድርግላቸው፤ አሮንና ልጆቹ ወደ መቅደሱ ይግቡ፤ እያንዳንዱንም ሰው በየሥራው ላይ ይደልድሉት፤ ምን መሸከም እንዳለበትም ያስታውቁት።

20. ቀዓታውያን ግን ንዋየ ቅዱሳቱን ለአንድ አፍታ እንኳን ለማየት አይግቡ፤ ቢገቡ ይሞታሉ።”

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ዘኁልቍ 4