ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ዘፀአት 29:6-16 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

6. መጠምጠሚያውን በራሱ ላይ በማድረግ የተቀደሰውን አክሊል ከመጠምጠሚያው ጋር አያይዘው።

7. ቅብዐ ዘይት ወስደህ በራሱ ላይ በማፍሰስ ቅባው።

8. ወንዶች ልጆቹን አምጥተህ ሸሚዞች አልብሳቸው።

9. የራስ ማሰሪያዎችንም አድርግላቸው፤ ከዚያም አሮንንና ወንዶች ልጆቹን መታጠቂያዎችን አስታጥቃቸው፤ ክህነት የዘላለም ሥርዐት ይሆንላቸዋል፤ በዚህም መንገድ አሮንንና ወንዶች ልጆቹን ትክናቸዋለህ።

10. “ወይፈኑን በመገናኛው ድንኳን ፊት ለፊት በማምጣት አሮንና ወንዶች ልጆቹ በራሱ ላይ እጆቻቸውን ይጫኑበት።

11. በመገናኛው ድንኳን ደጃፍ ላይ በእግዚአብሔር (ያህዌ) ፊት እረደው።

12. ከወይፈኑ ደም ወስደህ በመሠዊያው ቀንዶች ላይ በጣቶችህ አድርግበት፤ የቀረውንም ከመሠዊያው ሥር አፍሰው።

13. ከዚያም በሆድ ዕቃዎች ያለውን ስብ ሁሉ፣ የጉበቱን መሸፈኛና ሁለቱንም ኵላሊቶች በዙሪያቸው ካለው ስብ ጋር ወስደህ በመሠዊያው ላይ አቃጥላቸው።

14. ነገር ግን የወይፈኑን ሥጋ፣ ቆዳውንና የማይበላውን አሰስ ገሠስ ሥጋ ከሰፈር ውጭ አቃጥለው፤ የኀጢአት መሥዋዕት ነው።

15. “ከሁለቱ አውራ በጎች አንዱን ወስደህ፣ አሮንና ወንዶች ልጆቹ በራሱ ላይ እጃቸውን ይጭኑበታል።

16. አውራውንም በግ እረደው፤ ደሙንም ወስደህ በመሠዊያው ላይ ዙሪያውን እርጨው።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ዘፀአት 29