ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ዘፍጥረት 35:19-27 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

19. ራሔልም ሞተች፤ ወደ ኤፍራታ በሚወስደው መንገድ በቤተልሔም ተቀበረች።

20. ያዕቆብም በራሔል መቃብር ላይ ሐውልት አቆመ፤ እስከ ዛሬም የራሔል መቃብር ምልክት ይኸው ሐውልት ነው።

21. እስራኤልም ጒዞውን በመቀጠል ከጋዴር ወንዝ ባሻገር ድንኳኑን ተከለ።

22. እስራኤልም በዚያ ምድር ሳለ፣ ሮቤል ከአባቱ ቁባት ከባላ ጋር ተኛ፤ እስራኤልም ድርጊቱን ሰማ።ያዕቆብ ዐሥራ ሁለት ልጆች ነበሩት፤ እነርሱም፦

23. የልያ ልጆች፦የያዕቆብ የበኵር ልጅ ሮቤል፣ስምዖን፣ ሌዊ፣ ይሁዳ፣ ይሳኮር፣ ዛብሎን፤

24. የራሔል ልጆች፦ዮሴፍ፣ ብንያም፤

25. የራሔል አገልጋይ የባላ ልጆች፦ዳን፣ ንፍታሌም፤

26. የልያ አገልጋይ የዘለፋ ልጆች፦ጋድ፣ አሴር ናቸው።እነዚህ ያዕቆብ በሰሜን ምዕራብ መስጴጦምያ ሳለ የተወለዱለት ወንዶች ልጆች ነበሩ።

27. ያዕቆብ አባቱ ወዳለበት ወደ መምሬ መጣ፤ አብርሃምና ይስሐቅ የኖሩባት፣ ቂርያት አርባቅ ወይም ኬብሮን የተባለችው ቦታ ናት።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ዘፍጥረት 35