ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ዘፍጥረት 46:21-29 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

21. የብንያም ልጆች፦ቤላ፣ ቤኬር፣ አስቤል፣ ጌራ፣ ናዕማን፣አኪ፣ ሮስ፣ ማንፌንሑፊምና አርድ ናቸው።

22. እነዚህ ዐሥራ አራቱ፣ ራሔል ለያዕቆብ የወለደችለት ልጆችና የልጅ ልጆች ናቸው።

23. የዳን ልጅ፦ሑሺም ነው፤

24. የንፍታሌም ልጆች፦ያሕጽኤል፣ ጉኒ፣ ዬጽርና ሺሌም ናቸው፤

25. እነዚህ ሰባቱ ልጆች ሁሉ ላባ ለልጁ ለራሔል ከሰጣት ከባላ ላይ ያዕቆብ የወለዳቸው ናቸው።

26. ከያዕቆብ ጋር ወደ ግብፅ የሄዱት የገዛ ዘሮቹ ብዛት ሥልሳ ስድስት ሲሆን ይህ ቍጥር ግን የልጆቹን ሚስቶች አይጨምርም።

27. ዮሴፍ በግብፅ የወለዳቸውን ሁለት ልጆች ጨምሮ፣ ወደ ግብፅ የወረደው የያዕቆብ ቤተ ሰብ ቍጥር ሰባ ነበር።

28. ያዕቆብም ወደ ጌሤም ለመሄድ መመሪያን ይቀበል ዘንድ፣ ይሁዳን አስቀድሞ ወደ ዮሴፍ ላከው። እነርሱም ጌሤም ሲደርሱ፣

29. ዮሴፍ ሠረገላውን አዘጋጅቶ፤ አባቱን እስራኤልን ለመቀበል ወደ ጌሤም አመራ።ዮሴፍ አባቱ ዘንድ እንደ ደረሰ፣ ዐንገቱ ላይ ተጠምጥሞ ለረጅም ጊዜ አለቀሰ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ዘፍጥረት 46