ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሐዋርያት ሥራ 2:15-26 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

15. ጊዜው ገና ከጠዋቱ ሦስት ሰዓት ስለ ሆነ፣ እናንተ እንደምታስቡት እነዚህ ሰዎች አልሰከሩም።

16. ነገር ግን ይህ በነቢዩ በኢዩኤል እንዲህ ተብሎ የተነገረ ነው፤

17. “እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤ በመጨረሻው ቀን፣መንፈሴን በሥጋ ለባሽ ሁሉ ላይ አፈሳለሁ፤ወንዶችና ሴቶች ልጆቻችሁ ትንቢት ይናገራሉ፤ጒልማሶቻችሁ ራእይ ያያሉ፤ሽማግሌዎቻችሁ ሕልም ያልማሉ።

18. በዚያ ጊዜ በወንዶችና በሴቶች አገልጋዮቼ ላይ፣መንፈሴን አፈሳለሁ፤እነርሱም ትንቢት ይናገራሉ።

19. በላይ በሰማያት ድንቅ ነገሮችን፣አሳያለሁ፤ በታች በምድርም ምልክቶችን እሰጣለሁ፤ደምና እሳት፣ የጢስም ጭጋግ ይሆናል።

20. ታላቅና ክቡር የሆነው የጌታ ቀን ከመምጣቱ በፊት፣ፀሓይ ወደ ጨለማ፣ጨረቃም ወደ ደም ይለወጣሉ።

21. የጌታን ስም፣የሚጠራ ሁሉ ይድናል።’

22. “የእስራኤል ሰዎች ሆይ፤ ይህን ቃል ስሙ፤ እናንት ራሳችሁ እንደምታውቁት፣ እግዚአብሔር በመካከላችሁ ታምራትን፣ ድንቅ ነገሮችንና ምልክቶችን በእርሱ በኩል በማድረግ ለናዝሬቱ ኢየሱስ መስክሮለታል።

23. እግዚአብሔር በጥንት ውሳኔውና በቀደመው ዕውቀቱ ይህን ሰው አሳልፎ በእጃችሁ ሰጣችሁ፤ እናንተም በክፉ ሰዎች እጅ ሰቅላችሁ ገደላችሁት።

24. እግዚአብሔር ግን የሞትን ጣር አስወግዶ አስነሣው፤ ሞት ይዞ ሊያስቀረው አልቻለምና።

25. ዳዊትም ስለ እርሱ እንዲህ ይላል፤“ ‘ጌታን ሁል ጊዜ በፊቴ አየዋለሁ፤እርሱ በቀኜ ነውና፣ከቶ አልታወክም።

26. ስለዚህ ልቤ ደስ አለው፤ አንደበቴም ሐሤት አደረገ፤ሥጋዬም በተስፋ ይኖራል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሐዋርያት ሥራ 2