ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሮሜ 10:18-21 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

18. ነገር ግን አልሰሙ ይሆን? ብዬ እጠይቃለሁ፤ በርግጥ ሰምተዋል፤“ድምፃቸው በምድር ሁሉ፣ቃላቸውም እስከ ዓለም ዳርቻ ተሰማ።”

19. ደግሜም እጠይቃለሁ፤ እስራኤል አላስተዋሉ ይሆን? በቅድሚያ ሙሴ እንዲህ ይላል፤“ሕዝብ ባልሆኑት አስቀናቸዋለሁ፤ማስተዋል በሌለው ሕዝብ አስቈጣቸዋለሁ”

20. ኢሳይያስም በድፍረት፣“ላልፈለጉኝ ተገኘሁ፤ላልጠየቁኝ ራሴን ገለጥሁላቸው” ይላል።

21. ስለ እስራኤል ግን፣“ወደማይታዘዝና እሺ ወደማይል ሕዝብ፣ቀኑን ሙሉ እጄን ዘረጋሁ” ይላል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሮሜ 10