ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሮሜ 11:29-35 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

29. የእግዚአብሔር ስጦታና ጥሪ ጸጸት የለበትም።

30. እናንተም ቀድሞ ለእግዚአብሔር የማትታዘዙ እንደ ነበራችሁ፣ ከእነርሱ አለመታዘዝ የተነሣ አሁን ምሕረት እንዳገኛችሁ ሁሉ፣

31. እግዚአብሔር ለእናንተ ምሕረት ከማድረጉ የተነሣ፣ እነርሱም ምሕረት ያገኙ ዘንድ አሁን የማይታዘዙ ልጆች ሆነዋል፤

32. እግዚአብሔር ለሁሉም ምሕረት ያደርግ ዘንድ ሰውን ሁሉ ባለመታዘዝ ዘግቶታልና።

33. የእግዚአብሔር የጥበቡና የዕውቀቱ ባለጠግነት እንዴት ጥልቅ ነው!ፍርዱ አይመረመርም፤ለመንገዱም ፈለግ የለው … 

34. “የጌታን ልብ ያወቀ ማነው?አማካሪውስ የነበረ ማን ነው?”

35. “እግዚአብሔር መልሶ እንዲሰጠው፣ለእግዚአብሔር ያበደረ ከቶ ማን ነው?”

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሮሜ 11