ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ሆሴዕ 13:8-16 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

8. ግልገሎቿን እንደ ተነጠቀች ድብ፣እመታቸዋለሁ፤ እዘነታትላቸዋለሁ።እንደ አንበሳም ሰልቅጬ እውጣቸዋለሁ፤የዱር አራዊትም ይገነጣጥላቸዋል።

9. “እስራኤል ሆይ፤ በእኔ ላይ ስለ ተነሣህ፣ረዳትህንም ስለ ተቃወምህ ትጠፋለህ።

10. “ንጉሥንና አለቆችን ስጠኝ፤”ብለህ እንደ ጠየቅኸው፣ያድንህ ዘንድ ንጉሥህ የት አለ?በከተሞችህ ሁሉ የነበሩ ገዦችህስ የት አሉ?

11. በቊጣዬ ንጉሥን ሰጠሁህ፤በመዓቴም ሻርሁት።

12. የኤፍሬም በደል ተከማችቶአል፤ኀጢአቱም በመዝገብ ተይዞአል።

13. በምጥ ላይ እንዳለች ሴት ጭንቅ ይመጣበታል፤እርሱ ግን ጥበብ የሌለው ልጅ ነው፤የሚወለድበት ጊዜ ሲደርስ፣ከእናቱ ማሕፀን መውጣት የማይፈልግ ሕፃን ነው።

14. “ከመቃብር ኀይል እታደጋቸዋለሁ፤ከሞትም እቤዣቸዋለሁ፤ሞት ሆይ፤ መቅሠፍትህ የት አለ?መቃብር ሆይ፤ ማጥፋትህ የት አለ?“ከእንግዲህ ወዲህ አልራራለትም፤

15. በወንድሞቹ መካከል ቢበለጽግም እንኳ፣የምሥራቅ ነፋስ ከምድረ በዳ እየነፈሰ፣ ከእግዚአብሔር ዘንድ ይመጣል፤ምንጩ ይነጥፋል፤የውሃ ጒድጓዱም ይደርቃል።የከበረው ሀብቱ ሁሉ፣ከግምጃ ቤቱ ይበዘበዛል።

16. የሰማርያ ሰዎች በደላቸውን ይሸከማሉ፤በአምላካቸው ላይ ዐምፀዋልና፤በሰይፍ ይወድቃሉ፤ሕፃኖቻቸውም በምድር ላይ ይፈጠፈጣሉ፤የእርጉዝ ሴቶቻቸውም ሆድ ይቀደዳል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ሆሴዕ 13