ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 119:128-140 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

128. መመሪያህ ሙሉ በሙሉ ልክ ነው አልሁ፤ስለዚህ የሐሰትን መንገድ ሁሉ ጠላሁ።

129. ምስክርነትህ ሁሉ ድንቅ ነው፤ስለዚህ ነፍሴ ትጠብቀዋለች።

130. የቃልህ ትርጓሜ ያበራል፤አላዋቂዎችንም አስተዋዮች ያደርጋል።

131. ትእዛዝህን ናፍቄአለሁና፣አፌን ከፈትሁ፤ አለከለክሁም።

132. ስምህን ለሚወዱ ማድረግ ልማድህ እንደሆነ ሁሉ፣ወደ እኔ ተመልሰህ፣ ምሕረት አድርግልኝ።

133. አካሄዴን እንደ ቃልህ ቀና አድርግልኝ፤ኀጢአትም በላዬ እንዲሠለጥን አትፍቀድ።

134. ትእዛዝህን መጠበቅ እንድችል፣ከሰዎች ጥቃት ታደገኝ።

135. በባሪያህ ላይ ፊትህን አብራ፤ሥርዐትህንም አስተምረኝ።

136. ሕግህ ባለመከበሩ፤እንባዬ እንደ ውሃ ይፈሳል።

137. እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ጻድቅ ነህ፤ፍርድህም ትክክል ነው።

138. ምስክርነትህን በጽድቅ አዘዝህ፤እጅግ አስተማማኝም ነው።

139. ጠላቶቼ ቃልህን ዘንግተዋልና፣ቅናት አሳረረኝ።

140. ቃልህ እጅግ የነጠረ ነው፤ባሪያህም ወደደው።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 119