ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 119:13-27 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

13. ከአንደበትህ የሚወጣውን ደንብ ሁሉ፣በከንፈሬ እናገራለሁ።

14. ሰው በሀብቱ ብዛት ደስ እንደሚለው፣ምስክርነትህን በመከተል ደስ ይለኛል።

15. ድንጋጌህን አሰላስላለሁ፤ልቤን በመንገድህ ላይ ጥያለሁ።

16. በሥርዐትህ ደስ ይለኛል፤ቃልህንም አልዘነጋም።

17. ሕያው እንድሆን፣ ቃልህንም እንድጠብቅ፣ለአገልጋይህ መልካም አድርግ።

18. ከሕግህ ድንቅ ነገርን እንዳይ፣ዐይኖቼን ክፈት።

19. እኔ በምድር ላይ መጻተኛ ነኝ፤ትእዛዛትህን ከእኔ አትሰውር።

20. ዘወትር ደንብህን በመናፈቅ፣ነፍሴ እጅግ ዛለች።

21. ከትእዛዛትህ የሳቱትን፣እብሪተኞችንና ርጉሞችን ትገሥጻለህ።

22. ምስክርነትህን ጠብቄአለሁና፣ስድብንና ንቀትን ከእኔ አርቅ።

23. ገዦች ተቀምጠው ቢዶልቱብኝ እንኳ፣አገልጋይህ ሥርዐትህን ያሰላስላል።

24. ምስክርነትህ ለእኔ ደስታዬ ነው፤መካሪዬም ነው።

25. ነፍሴ ከዐፈር ተጣበቀች፤እንደ ቃልህ መልሰህ ሕያው አድርገኝ።

26. ስለ መንገዴ ገልጬ ነገርሁህ፤ አንተም መለስህልኝ፤ሥርዐትህን አስተምረኝ።

27. የድንጋጌህን መንገድ እንዳስተውል አድርገኝ፤እኔም ድንቅ ሥራህን አሰላስላለሁ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 119