ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 119:131-147 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

131. ትእዛዝህን ናፍቄአለሁና፣አፌን ከፈትሁ፤ አለከለክሁም።

132. ስምህን ለሚወዱ ማድረግ ልማድህ እንደሆነ ሁሉ፣ወደ እኔ ተመልሰህ፣ ምሕረት አድርግልኝ።

133. አካሄዴን እንደ ቃልህ ቀና አድርግልኝ፤ኀጢአትም በላዬ እንዲሠለጥን አትፍቀድ።

134. ትእዛዝህን መጠበቅ እንድችል፣ከሰዎች ጥቃት ታደገኝ።

135. በባሪያህ ላይ ፊትህን አብራ፤ሥርዐትህንም አስተምረኝ።

136. ሕግህ ባለመከበሩ፤እንባዬ እንደ ውሃ ይፈሳል።

137. እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ጻድቅ ነህ፤ፍርድህም ትክክል ነው።

138. ምስክርነትህን በጽድቅ አዘዝህ፤እጅግ አስተማማኝም ነው።

139. ጠላቶቼ ቃልህን ዘንግተዋልና፣ቅናት አሳረረኝ።

140. ቃልህ እጅግ የነጠረ ነው፤ባሪያህም ወደደው።

141. እኔ ታናሽና የተናቅሁ ነኝ፤ነገር ግን መመሪያህን አልዘነጋሁም።

142. ጽድቅህ ዘላለማዊ ጽድቅ ነው፤ሕግህም እውነት ነው።

143. መከራና ሥቃይ ደርሶብኛል፤ነገር ግን ትእዛዝህ ደስታዬ ነው።

144. ምስክርነትህ ለዘላለም የጽድቅ ምስክርነት ነው፤በሕይወት እኖር ዘንድ ማስተዋልን ስጠኝ።

145. እግዚአብሔር ሆይ፤ በፍጹም ልቤ እጮኻለሁና መልስልኝ፤ሥርዐትህንም እጠብቃለሁ።

146. ወደ አንተ እጣራለሁና አድነኝ፤ምስክርነትህንም እጠብቃለሁ።

147. ትረዳኝ ዘንድ ጎሕ ሳይቀድ ተነሥቼ እጮኻለሁ፤ቃልህንም ተስፋ አደርጋለሁ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 119