ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 119:164-172 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

164. ጻድቅ ስለ ሆነው ሕግህ፤በቀን ሰባት ጊዜ አመሰግንሃለሁ።

165. ሕግህን የሚወዱ ብዙ ሰላም አላቸው፤ዕንቅፋትም የለባቸውም።

166. እግዚአብሔር ሆይ፤ ማዳንህን ተስፋ አደርጋለሁ፤ትእዛዝህንም እፈጽማለሁ።

167. ነፍሴ ምስክርነትህን ትጠብቃለች፤እጅግ እወደዋለሁና።

168. መንገዴ ሁሉ በፊትህ ግልጽ ነውና፣ሕግህንና ምስክርነትህን እጠብቃለሁ።

169. እግዚአብሔር ሆይ፤ ጩኸቴ ከፊትህ ይድረስ፤እንደ ቃልህም ማስተዋልን ስጠኝ።

170. ልመናዬ ከፊትህ ይድረስ፤እንደ ቃልህም ታደገኝ።

171. ሥርዐትህን አስተምረኸኛልና፣ከንፈሮቼ ምስጋናን አፈለቁ።

172. ትእዛዛትህ ሁሉ የጽድቅ ትእዛዛት ናቸውና፣አንደበቴ ስለ ቃልህ ይዘምር።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 119