ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 119:22-36 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

22. ምስክርነትህን ጠብቄአለሁና፣ስድብንና ንቀትን ከእኔ አርቅ።

23. ገዦች ተቀምጠው ቢዶልቱብኝ እንኳ፣አገልጋይህ ሥርዐትህን ያሰላስላል።

24. ምስክርነትህ ለእኔ ደስታዬ ነው፤መካሪዬም ነው።

25. ነፍሴ ከዐፈር ተጣበቀች፤እንደ ቃልህ መልሰህ ሕያው አድርገኝ።

26. ስለ መንገዴ ገልጬ ነገርሁህ፤ አንተም መለስህልኝ፤ሥርዐትህን አስተምረኝ።

27. የድንጋጌህን መንገድ እንዳስተውል አድርገኝ፤እኔም ድንቅ ሥራህን አሰላስላለሁ።

28. ነፍሴ በሐዘን ተዝለፈለፈች፤እንደ ቃልህ አበርታኝ።

29. የሽንገላን መንገድ ከእኔ አርቅ፤ሕግህን በጸጋህ ስጠኝ።

30. የእውነትን መንገድ መርጫለሁ፤ሕግህንም ፊት ለፊቴ አድርጌአለሁ።

31. እግዚአብሔር ሆይ፤ ከምስክርነትህ ጋር ተጣብቄአለሁ፤አሳልፈህ ለውርደት አትስጠኝ።

32. ልቤን አስፍተህልኛልና፣በትእዛዛትህ መንገድ እሮጣለሁ።

33. እግዚአብሔር ሆይ፤ የሥርዐትህን መንገድ አስተምረኝ፤እኔም እስከ መጨረሻው እጠብቀዋለሁ።

34. ሕግህን እንድጠብቅ፣ በፍጹም ልቤም እንድታዘዘው፣ ማስተዋልን ስጠኝ።

35. በእርሷ ደስ ይለኛልና፣በትእዛዝህ መንገድ ምራኝ።

36. ከራስ ጥቅም ይልቅ፣ልቤን ወደ ምስክርነትህ አዘንብል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 119