ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 119:4-15 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

4. ጠንቅቀን እንጠብቃት ዘንድ፣አንተ ሥርዐትን አዘሃል።

5. ሥርዐትህን እጠብቅ ዘንድ፣ምነው መንገዴ ጽኑ በሆነልኝ ኖሮ!

6. ወደ ትእዛዛትህ ስመለከት፣በዚያን ጊዜ አላፍርም።

7. የጽድቅ ፍርድህን ስማር፣በቅን ልብ ምስጋና አቀርብልሃለሁ።

8. ሥርዐትህን እጠብቃለሁ፤ፈጽመህ አትተወኝ።

9. ጒልማሳ መንገዱን እንዴት ያነጻል?በቃልህ መሠረት በመኖር ነው።

10. በሙሉ ልቤ ፈለግሁህ፤ከትእዛዛትህ ፈቀቅ እንዳልል አድርገኝ።

11. አንተን እንዳልበድል፣ቃልህን በልቤ ሰወርሁ።

12. እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ ቡሩክ ነህ፤ሥርዐትህን አስተምረኝ።

13. ከአንደበትህ የሚወጣውን ደንብ ሁሉ፣በከንፈሬ እናገራለሁ።

14. ሰው በሀብቱ ብዛት ደስ እንደሚለው፣ምስክርነትህን በመከተል ደስ ይለኛል።

15. ድንጋጌህን አሰላስላለሁ፤ልቤን በመንገድህ ላይ ጥያለሁ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 119