ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 119:58-67 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

58. በፍጹም ልቤ ፊትህን ፈለግሁ፤እንደ ቃልህ ቸርነትህን አሳየኝ።

59. መንገዴን ቃኘሁ፤አካሄዴንም ወደ ምስክርህ አቀናሁ።

60. ትእዛዝህን ለመጠበቅ፣ቸኰልሁ፤ አልዘገየሁምም።

61. የክፉዎች ገመድ ተተበተበብኝ፤ እኔ ግን ሕግህን አልረሳሁም።

62. ስለ ጻድቅ ሥርዐትህ፣በእኩለ ሌሊት ላመሰግንህ እነሣለሁ።

63. እኔ ለሚፈሩህ ሁሉ፣ሥርዐትህንም ለሚጠብቁ ባልንጀራ ነኝ።

64. እግዚአብሔር ሆይ፤ ምድር በምሕረትህ ተሞላች፤ሥርዐትህን አስተምረኝ።

65. እግዚአብሔር ሆይ፤ እንደ ቃልህ፣ለአገልጋይህ በጎ ውለሃል።

66. በትእዛዛትህ አምናለሁና፣ በጎ ማስተዋልንና ዕውቀትንአስተምረኝ።

67. እንዲያው ሳይቸግረኝ መንገድ ስቼ ሄድሁ፤አሁን ግን ቃልህን እጠብቃለሁ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 119