ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 119:59-73 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

59. መንገዴን ቃኘሁ፤አካሄዴንም ወደ ምስክርህ አቀናሁ።

60. ትእዛዝህን ለመጠበቅ፣ቸኰልሁ፤ አልዘገየሁምም።

61. የክፉዎች ገመድ ተተበተበብኝ፤ እኔ ግን ሕግህን አልረሳሁም።

62. ስለ ጻድቅ ሥርዐትህ፣በእኩለ ሌሊት ላመሰግንህ እነሣለሁ።

63. እኔ ለሚፈሩህ ሁሉ፣ሥርዐትህንም ለሚጠብቁ ባልንጀራ ነኝ።

64. እግዚአብሔር ሆይ፤ ምድር በምሕረትህ ተሞላች፤ሥርዐትህን አስተምረኝ።

65. እግዚአብሔር ሆይ፤ እንደ ቃልህ፣ለአገልጋይህ በጎ ውለሃል።

66. በትእዛዛትህ አምናለሁና፣ በጎ ማስተዋልንና ዕውቀትንአስተምረኝ።

67. እንዲያው ሳይቸግረኝ መንገድ ስቼ ሄድሁ፤አሁን ግን ቃልህን እጠብቃለሁ።

68. አንተ መልካም ነህ፤ የምታደርገው መልካም ነው፤እንግዲህ ሥርዐትህን አስተምረኝ።

69. እብሪተኞች ስሜን በሐሰት አጠፉ፤እኔ ግን ትእዛዝህን በፍጹም ልብ እጠብቃለሁ።

70. ልባቸው የሠባና የደነደነ ነው፤እኔ ግን በሕግህ ደስ ይለኛል።

71. ሥርዐትህን እማር ዘንድ፣በመከራ ውስጥ ማለፌ መልካም ሆነልኝ።

72. ከአእላፋት ብርና ወርቅ ይልቅ፣ከአፍህ የሚወጣው ሕግ ይሻለኛል።

73. እጆችህ ሠሩኝ፤ አበጃጁኝም፤ትእዛዛትህን እንድማር ማስተዋልን ስጠኝ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 119