ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

መዝሙር 119:92-100 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

92. ሕግህ ደስታዬ ባይሆን ኖሮ፣በመከራዬ ወቅት በጠፋሁ ነበር።

93. በእርሱ ሕያው አድርገኸኛልና፣ትእዛዝህን ከቶ አልረሳም።

94. እኔ የአንተ ነኝ፤ እባክህ አድነኝ፤ሕግህንም ፈልጌአለሁና።

95. ክፉዎች ሊያጠፉኝ አድብተዋል፤እኔ ግን ምስክርነትህን አሰላስላለሁ።

96. ለፍጹምነት ሁሉ ዳርቻ እንዳለው አየሁ፤ትእዛዝህ ግን እጅግ ሰፊ ነው።

97. አቤቱ፤ ሕግህን ምንኛ ወደድሁ!ቀኑን ሙሉ አሰላስለዋለሁ።

98. ትእዛዛትህ ምንጊዜም ስለማይለዩኝ፣ከጠላቶቼ ይልቅ አስተዋይ አደረጉኝ።

99. ምስክርነትህን አሰላስላለሁና፣ከአስተማሪዎቼ ሁሉ የላቀ አስተዋይ ልብ አገኘሁ።

100. መመሪያህን ተከትዬ እሄዳለሁና፣ከሽማግሌዎች ይልቅ አስተዋይ ሆንሁ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ መዝሙር 119