ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ዘኁልቍ 24:10-17 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

10. ከዚያም ባላቅ፣ በበለዓም ላይ እጅግ ተቈጣ፤ እጆቹንም አጨብጭቦ እንዲህ አለው፤ “ጠላቶቼን እንድትረግምልኝ ጠራሁህ፤ አንተ ግን ሦስቱንም ጊዜ ባረክሃቸው።

11. በል ቶሎ ወደ ቤትህ ሂድልኝ፤ ወሮታህን አሳምሬ ልከፍልህ ነበር፤ እግዚአብሔር (ያህዌ) ግን እንዳታገኝ ከለከለህ።”

12. በለዓምም ለባላቅ እንዲህ ሲል መለሰለት፤ ወደ እኔ ለላክሃቸው ሰዎች እንዲህ ብዬ ነግሬአቸው አልነበረምን?

13. ‘ሌላው ይቅርና ባላቅ በብርና በወርቅ የተሞላ ቤተ መንግሥቱን ቢሰጠኝ እንኳ፣ እግዚአብሔር (ያህዌ) የሚለውን ብቻ ከመናገር በስተቀር ከእግዚአብሔር (ያህዌ) ትእዛዝ ውጭ በራሴ ሐሳብ በጎም ሆነ ክፉ ማድረግ አልችልም።’

14. እንግዲህ ወደ ሕዝቤ እመለሳለሁ፤ ይሁን እንጂ በሚመጣው ዘመን ይህ ሕዝብ በሕዝብህ ላይ የሚያደርገውንና ልንገርህ።”

15. ከዚያም እንዲህ ሲል ንግሩን ጀመረ፤“የቢዖር ልጅ የበለዓም ንግር፤የዚያ ዐይኑ የተከፈተለት ሰው ንግር።

16. የዚያ የአምላክን (ኤሎሂም) ቃል የሚሰማ፣ከልዑልም ዕውቀትን ያገኘው፣ሁሉን ከሚችለው ራእይ የሚገለጥለት፣መሬት የተደፋው፣ ዐይኖቹም የተገለጡለት ሰው ንግር፤

17. “አየዋለሁ፤ አሁን ግን አይደለም፤እመለከተዋለሁ፤ በቅርቡ ግን አይደለም፤ኮከብ ከያዕቆብ ይወጣል፤በትረ መንግሥት ከእስራኤል ይነሣል።የሞዓብን ግንባሮች፣የሤትንም ወንዶች ልጆች ራስ ቅል ያደቃል።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ዘኁልቍ 24