ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

ዘፍጥረት 49:9-24 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

9. “አንተ የአንበሳ ደቦል ይሁዳ፤ከዐደንህ የምትመለስ ልጄ፣እንደ አንበሳ ያደፍጣል፤ በምድርም ላይ ይተኛል፤እንደ እንስት አንበሳም ያደባል፤ታዲያ ማን ሊቀሰቅሰው ይደፍራል?

10. በትረ መንግሥት ከይሁዳ እጅ አይወጣም፤የገዥነት ምርኵዝም ከእግሮቹ መካከል።ገዥነት የሚገባው እስኪመጣ ድረስ፣ሕዝቦች ሁሉ ይታዘዙታል።

11. አህያውን በወይን ግንድ፣ውርንጫውንም በምርጡ የወይን ሐረግቅርንጫፍ ላይ ያስራል፤ልብሱን በወይን ጠጅ፣መጐናጸፊያውንም በወይን ጭማቂ ያጥባል።

12. ዐይኖቹ ከወይን ጠጅ የቀሉ፣ጥርሶቹም ከወተት ይልቅ የነጡ ይሆናሉ።

13. “ዛብሎን፣ በባሕር ዳር ይኖራል፤የመርከቦች መጠጊያም ይሆናል፤ወሰኑም እስከ ሲዶና ይደርሳል።

14. “ይሳኮር፣ ዐጥንተ ብርቱ አህያ፣በጭነት መካከል የሚተኛ፣

15. ማረፊያ ቦታው መልካም፣ምድሪቱም አስደሳች መሆኗን ሲያይ፣ትከሻውን ለሸክም ያመቻቻል፤ተገድዶም ያገለግላል።

16. “ዳን፣ ከእስራኤል ነገዶች እንደ አንዱ ሆኖ፣በራሱ ሕዝብ ላይ ይፈርዳል።

17. ዳን የመንገድ ዳር እባብ፣የመተላለፊያም መንገድ እፉኝት ነው፤ጋላቢው የኋሊት እንዲወድቅ፣የፈረሱን ሰኮና ይነክሳል።

18. “እግዚአብሔር ሆይ (ያህዌ)፤ ማዳንህን እጠባበቃለሁ።

19. “ጋድን ወራሪዎች አደጋ ይጥሉበታል፤እርሱ ግን ዱካቸውን ተከታትሎ ብድሩን ይመልሳል።

20. “አሴር ማእደ ሰፊ ይሆናል፤ለነገሥታትም የሚስማማ ምግብ ያቀርባል።

21. “ንፍታሌም ነጻ እንደ ተለቀቀች፣የሚያማምሩም ግልገሎችእንደምትወልድ ሚዳቋ ነው።

22. ዮሴፍ፤ ፍሬያማ የወይን ተክል፣በምንጭ ዳር የተተከለ ወይን ነው።ሐረጎቹ ቅጥርን ያለብሳሉ።

23. ቀስተኞች በጭካኔ አጠቁት፤በጥላቻም ነደፉት።

24. ነገር ግን በያዕቆብ ኀያል አምላክ ክንድ፣እረኛው በሆነው በእስራኤል ዐለት፣ ቀስቱ ጸና፤ጠንካራ ክንዱም ቀለጠፈ።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ ዘፍጥረት 49