ብሉይ ኪዳን

አዲስ ኪዳን

አሞጽ 9:11-15 መጽሐፍ ቅዱስ፥ አዲሱ መደበኛ ትርጒም (NASV)

11. “በዚያ ቀን፣የወደቀውን የዳዊትን ድንኳን አነሣለሁ፤የተሰበረውን እጠግናለሁ፤የፈረሰውን ዐድሳለሁ፤ቀድሞ እንደነበረም አድርጌ እሠራዋለሁ፤

12. ስለዚህ የኤዶምን ትሩፍ፣በስሜ የተጠሩትንም ሕዝቦች ሁሉ ይወርሳሉ፤”ይላል ይህን የሚያደርግ እግዚአብሔር።

13. እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፤“እነሆ፤ ዐጫጁ ዐጭዶ ሳይጨርስ፣ዐራሹ በላዩ የሚደርስበት፣ችግኝ ተካዩም ገና ተክሎ ሳይጨርስ፣ወይን ጨማቂው የሚደርስበት ጊዜ ይመጣል፤አዲስ የወይን ጠጅ ከተራሮች ይንጠባጠባል፤ከኰረብቶችም ሁሉ ይፈሳል።

14. የተሰደደውን ሕዝቤን እስራኤልን እመልሳለሁ፤እነርሱም የፈራረሱትን ከተሞች መልሰው ሠርተው በውስጣቸው ይኖራሉ።የወይን ተክል ተክለው፣ ጠጁን ይጠጣሉ፤አትክልት ተክለው ፍሬውን ይበላሉ።

15. እስራኤልን በገዛ ምድራቸው እተክላቸዋለሁ፤ከሰጠኋቸውም ምድር፣ ዳግመኛአይነቀሉም”ይላል አምላክህ እግዚአብሔር።

ሙሉ ምዕራፍ ማንበብ አሞጽ 9